Fana: At a Speed of Life!

የዒድ አልፈጥር በዓል ተከበረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 1 ሺህ 446ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ተከብሯል።

የዒድ አልፈጥር በዓል በመላው ኢትዮጵያ በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ነው የተከበረው።

በዓሉ በተለያዩ ከተሞች በድምቀት የተከበረ ሲሆን÷ሕዝበ ሙስሊሙ በማክበሪያ ሥፍራዎች በመገኘት የዒድ ሶላት ሥነ-ሥርዓት አካሂዷል።

በታላቁ የረመዳን ወር መጨረሻ የሚከበረውን የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም፣ በመተሳሰብና የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ማሳለፍ እንደሚገባ የፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍ/ቤት ጥሪ አቅርቧል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.