ሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘላቂ ሰላምና ብልፅግናን ዕውን ለማድረግ ተሳትፎውን ሊያጠናክር እንደሚገባ ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘላቂ ሰላምና ብልፅግናን ዕውን ለማድረግ በሚከናወኑ ተግባራት ተሳትፎውን አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ ገለጹ።
1 ሺህ 446ኛው የዒድ አል ፈጥር በዓል በድሬዳዋ ከተማ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ ተከብሮ ተጠናቅቋል፡፡
ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ በዚህ ወቅት ÷ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘላቂ ሰላምና ብልፅግናን ዕውን ለማድረግ አበረታች ሥራዎች እያከናወነ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡
ሙስሊሙ ማህበረሰብ ተሳትፎውን ወደ ላቀ ደረጃ በማሳደግ ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማፅናት ይበልጥ መስራት እንደሚጠበቅበት ጠቁመው÷ በረመዳን ፆም የታዩት የመረዳዳትና የመደጋገፍ ተግባራት በቀጣይም ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አመልክተዋል።
የድሬዳዋ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ አብዱላሂ መሐመድ በበኩላቸው÷ በዓሉን ስናከብር የተቸገሩትን በመርዳት እና የታመሙትን በመጠየቅ መሆን ይኖርበታል ብለዋል።
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የአንድነት እንዲሆን ተመኝተው÷ ህዝበ ሙስሊሙ በድሬዳዋ ሁለንተናዊ የለውጥ ጉዞ ውስጥ እያበረከተ የሚገኘውን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ የድርሻውን መወጣት እንዳለበት መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡