ምክር ቤቱ ነገ የፌደራል መንግሥት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ሥርዓት ለመደንገግ የወጣ ማሻሻያ አዋጅን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ መጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም 22ኛ መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል፡፡
ምክር ቤቱ በመደበኛ ስብሰባው የፌደራል መንግስት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ሥርዓት ለመደንገግ የወጣ ማሻሻያ አዋጅ ላይ ተወያይቶ አዋጁን ያጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የም/ቤቱ መረጃ ያመላክታል፡፡