Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያና የዓለም ባንክ የ96 ነጥብ 367 ሚሊየን ዶላር የድጋፍና ብድር ስምምነት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ እና የዓለም ባንክ የትምህርት ዘርፉን ለማሻሻል የሚውል የ96 ነጥብ 367 ሚሊየን ዶላር ወይም የ12 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር የድጋፍ እና ብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ እና በዓለም ባንክ የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ማሪያም ሳሊም ተፈራርመዋል፡፡

ከተፈረመው ስምምነት ውስጥ 50 ሚሊየን ዶላሩ ከዓለም አቀፉ የልማት ማህበር በብድር መልክ የተሰጠ ሲሆን÷ 46 ነጥብ 367 ሚሊየን ዶላሩ ደግሞ ከዓለም አቀፉ የትምህርት አጋርነት ፈንድ በድጋፍ የተገኘ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ድጋፉ የቅድመ መደበኛ እና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርትን ተደራሽ ለማድረግ የሚውል ነው መባሉን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

በተለይም ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል ደረጃ ያሉ መምህራንን አቅም ለመገንባት እንዲሁም ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ጋር በተጣጣመ መልኩ የቅደመ መምህርነት ስልጠናዎችን ለመስጠት እንደሚውል ተጠቁሟል፡፡

በተጨማሪም የትምህርት ቤት አመራሮችን አቅም ለማጎልበት፣ የሴት አመራሮችን ለመደገፍ እና በዲጂታል የታገዘ ሥርዓት ትምህርትን ለመገንባት የሚያግዝ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.