Fana: At a Speed of Life!

ከ224 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የመጠጥ ውሃ ግንባታ ለማካሄድ የውል ስምምነት ተፈረመ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በ224 ሚሊየን 784 ሺህ ብር ወጭ የመጠጥ ውሃ ግንባታ ለማካሄድ የውል ስምምነት ተፈራርሟል።

በዋን ዋሽ ፕሮግራም የያያ ወርቄ ሲአር ዋሽ ባለብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ራያ ቆቦ ወረዳ የሚገነባ ሲሆን÷ ጀማል አህመድ ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ የውል ስምምነት መውሰዱ ተመላክቷል።

የመጠጥ ውሃ ግንባታው በ15 ወራት ተጠናቅቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ውል መገባቱም ተገልጿል።

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከ13 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል።

ስምምነቱን የተፈራረሙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) የሕብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ በተገባው የውል ስምምነት መሰረት በሚፈለገው የጥራት ደረጃ እና በተቀመጠው ጊዜ ፕሮጀክቱን ማጠናቀቅ እንደሚገባ አሳስበዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.