የግብርና ዘርፉን ማዘመን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ያግዛል – ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የግብርና ዘርፉን ማዘመን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ሀገር አቀፍ የግብርና ባለሙያዎች የክህሎት ልማት ሥልጠና መርሐ ግብር ዛሬ በኮምቦልቻ ከተማ ተጀምሯል፡፡
በማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ÷ በሀገር አቀፍ ደረጃ 70 ሺህ የልማት ጣቢያ ሰራተኞች መኖራቸውን አንስተዋል፡፡
በዛሬው ዕለትም 1 ሺህ 300 የሚሆኑ የልማት ጣቢያ ሰራተኞች በይፋ የደረጃ ማሻሻያ ስልጠና መጀመራቸውን ጠቅሰዋል፡፡
የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የግብርና ዘርፉን ማዘመንና በእውቀት መደገፍ ይገባል ያሉት ሚኒስትሩ÷ ለግብርና ጣቢያ ሰራተኞች የሚሰጠው ስልጠና ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አመልክተዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በበኩላቸው ሀገር ትለወጥ ዘንድ በእውቀት የተደገፈ ትውልድ መቅረጽ እንደሚያስፈልግ ገልጸው÷ ግብርናውን ለማዘመን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በከድር መሃመድ