Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ እና ቱርክሜኒስታን ግንኙነታቸውን ማጠናከር በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) እና የቱርክሜኒስታን አቻቸው ረሺድ ምሬዶቭ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል፡፡

ሚኒስትሮቹ በስልክ ባደረጉት በውይይት÷ የሁለቱን ሀገራት ትብብር በኢኮኖሚያዊ ዘርፍ ለማሳደግ ብሎም የሀገራቱን የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ውይይት ማጎልበት፣ ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር መተባበርን እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ከመፍጠር አንጻር በጋራ ለመስራት ያላቸውን ፍላጎት ገልጸዋል፡፡

ሁለቱ ሀገራት ዘርፈ ብዙ እና ዘላቂ ግንኙነትን ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸው÷ የሀገራቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጉብኝት እንዲደረግ ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ተስማምተዋል፡፡

ሚኒስትሮቹ ኢትዮጵያ እና ቱርክሜኒስታን በኢኮኖሚው ዘርፍ፣ በቀጣናዊ መረጋጋት እና ትብብር ላይ በጋራ ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት መግለጻቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.