Fana: At a Speed of Life!

አየር መንገዱ የአውሮፕላን መቀመጫዎችን ለመግዛት ስምምነት ተፈራረመ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዜድ-400 የተሰኙ የአውሮፕላን መቀመጫዎችን ለመግዛት ሳፍራን ከተባለ የአውሮፕላን ቁሳቁስ አምራች ኩባንያ ጋር ስምምነት መፈራረሙን ገልጿል፡፡

በስምምነቱ መሰረት ኩባንያው ለአየር መንገዱ ስምንት የቦይንግ 777-9 አውሮፕላኖች ኢኮኖሚ ክፍል የሚሆኑ መቀመጫዎችን እንደሚያቀርብ ታውቋል፡፡

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የተመረጡት Z400 መቀመጫዎች ለተሳፋሪዎች የተሻለ ምቾት የሚሰጡ መሆናቸውንም ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.