Fana: At a Speed of Life!

ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) የቃሊቲ ሞዴል መናኸሪያ የግንባታ ሂደትን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒሰትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘውን የቃሊቲ ዘመናዊ ሀገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት ሞዴል መናኸሪያን ጎብኝተዋል፡፡

መናኸሪያው በሰዓት 120 አውቶቡሶችንና 7 ሺህ 200 ተሳፋሪዎችን የማስተናገድ አቅም እንዳለው ተገልጿል።

በውስጡ ካፍቴሪያዎች፣ ሱቆች፣ የስብሰባ አዳራሾች፣ የመመገቢያ ስፍራዎች፣ ከ1ሺህ 130 በላይ የማረፊያ ወንበሮችና የታክሲ ተርሚናል የተዘጋጀለት ማዕከል ነው ተብሏል።

የመናኸሪያው ግንባታ በ3 ነጥብ 9 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን፥ በውስጡ ለልዩ ልዩ አገልግሎት የሚውል ባለ አራት ወለል ህንፃ ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ መሆኑን የከንቲባ ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.