አርሰናል እና ብሬንትፎርድ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርሰናል እና ብሬንትፎርድ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
ምሽት 1፡30 ላይ በሜዳቸውና እና በደጋፊያቸው ፊት ብሬንትፎርንድን ያስተናገዱት መድፈኞቹ በድጋሚ ነጥብ ጥለዋል፡፡
አርሰናል በ61ኛው ደቂቃ ላይ ቶማስ ፓርቴ ባስቆጠረው ግብ መምራት ችሎ የነበረ ቢሆንም ዮአን ዊሳ በ73ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል።