Fana: At a Speed of Life!

በሐረሪ ክልል ለብሔራዊ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች የምሳ ግብዣ መርሐ-ግብር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሐረሪ ክልል ለሚገኙ ለብሔራዊ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ የምሳ ግብዣ መርሐ-ግብር ተካሂዷል።

በመርሐ-ግብሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ÷ ወጣቶቹ በተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራት ላይ በመሳተፍ እያደረጉት ያለውን ድጋፍ አድንቀዋል።

የብሔራዊ በጎ ፈቃድ ወጣቶች የሚሰጡት አገልግሎት የማህበረሰቡን ችግሮች በማቃለል አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡበት እንደሚገኝ ገልፀዋል።

በተለይ የብሔራዊ በጎ ፈቃድ መርሐ-ግብሩ ቀድሞ የነበረውን እርስ በርስ የመረዳዳት እሴቶችን በማጎልበት አበርክቶው የጎላ ነው ብለዋል፡፡

ለትንሳዔ በዓል የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት በማስተላለፍም÷ በዓሉን በወንድማማችነት መንፈስ በመደጋገፍ ማሳለፍ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በመርሐ-ግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የስራ አመራሮች እና የብሔራዊ በጎ ፈቃድ መርሀ-ግብር ተሳታፊ ወጣቶች መገኘታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.