ኢትዮጵያ በአውሶም የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ እየተሳተፈች ነው
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በዩጋንዳ እየተካሄደ በሚገኘው የአፍሪካ ኅብረት የሶማሊያ ድጋፍና ማረጋጋት ተልዕኮ (አውሶም) የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ እየተሳተፈች ነው፡፡
በስብሰባው የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) እና ሌሎች የሥራ ሃላፊዎች መገኘታቸውን በዩጋንዳ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡