Fana: At a Speed of Life!

ዶናልድ ትራምፕ እና ዘለንስኪ ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የዩክሬን አቻቸው ቮለድሚር ዘለንስኪ ዛሬ በጣሊያን ሮም ተገናኝተው ተወያይተዋል፡፡

ሁለቱ መሪዎች በዛሬው ዕለት በተከናወነው የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ የቀብር ሥነ ሥርዓተ ላይ ታድመዋል፡፡

ከሥነ ሥርዓቱ በኋላ ፍሬያማና ገንቢ ውይይት ማድረጋቸውንና ከሰዓታት በኋላም ውይይታቸው እንደሚቀጥል የሀገራቱን ባለስልጣናት ጠቅሶ ሮይተርስ ዘግቧል።

ሁለቱ መሪዎች ባለፈው የካቲት ወር አጋማሽ በነጩ ቤተ-መንግስት ተገናኝተው በከፍተኛ ንትርክ ያለስምምነት ከተለያዩ ወዲህ በአካል ሲገናኙ የዛሬው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.